ክብሩን፣ ድሉን፣ ውጤቱን፣ ምስጋናውን ፈጣሪ ይውሰድና፤ ማልደን የተነሳንበት ኢትዮጵያን በ600 ሚሊዮን ችግኞች አረንጓዴ የማልበስ ሕልም 615.7 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የታለመለትን ፍሬ በማፍራቱ እጅግ ደስ ብሎኛል ብለዋል አቶ አደም ፋራህ።ህፃናት፣ አረጋውያን፣ ሴቶች እና ወጣቶች ስለ ነገዋ ኢትዮጵያችን ብለው፣ ትውልድን አስበው አፈር እየማሱ ደፋ ቀና ሲሉ ማየት ልብን በሃሴት ይሞላል ነው ያሉት በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ።በዘር፣ በፆታ፣ በእድሜ፣ በሙያ ሳንከፋፈል ስለ ኢትዮጵያ እና ስለ ትውልዷ ብለን ዛሬ ላይ የሰራነው ገድል ነገ በታሪክ ዘንድ ወርቃማ ካባ እንደሚያጎናፅፈን ፈፅሞ ጥርጥር የለውም ብለዋል አቶ አደም ፋራህ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት የደስታ መግለጫ መልዕክት።ዛሬ የተከልነውንም ተንከባክበን በማፅደቅ፣ የአረንጓዴ አሻራ ትጋታችንን በእጥፍ በመጨመር የኢትዮጵያ ብልፅግና እና ስልጣኔ በዛፎች እና በተፈጥሯዊ በረከቶች መሀል እንዲዋቀር የበኩላችንን ኃላፊነት መወጣታችንን እንቀጥላለን፤ እንኳን ደስ አለን፣ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ኢትዮጵያን አረንጓዴ የማልበስ ሕልማችን የታለመለትን ፍሬ በማፍራቱ እጅግ ደስ ብሎኛል – አቶ አደም ፋራህ

More Stories
” የፕሬስ ነጻነት ቀን ስናከብር ዜጎች በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) መረጃ እንዳይጭበረበሩ ትክክለኛ መረጃ የሚያገኙበት እሳቤ የሚያጎላበት ቀን ሊሆን ይገባል፡፡”
አራተኛው ዙር የኢራን እና የአሜሪካ ድርድር ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ
የደቡብ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የስራ ኃላፊዎች የማሻ ቅርንጫፍ ጣቢያ የስራ አፈጻጸምን ተመለከቱ