በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ 490 ጋላክሲ ሳምሰንግ ሞባይል ስልኮች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
ፖሊስ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት ባደረገው ክትትል ሰኔ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል በአንድ ግለሰብ ሱቅ ውስጥ በህግ አግባብ በተደረገ ብርበራ ስልኮቹን መያዝ መቻሉ ተመላክቷል፡፡
የንግድ ምልክታቸው ጋላክሲ ሳምሰንግ የሆኑ እነዚህ 490 ሞባይል ስልኮች በሶስት ካርቶን ተደብቀው በኮንትሮባንድ ወደ ሀገር ቤት መግባታቸው ተገልጿል፡፡
ህጋዊነትን ያልተከተለ የንግድ አሰራር በሀገር ላይ የሚያስከትለው ኢኮኖሚያዊ ጉዳት እና በህጋዊ ነጋዴው ላይ የሚያሳድረው አሉታዊ ጫና ከፍተኛ እንደሆነ በመገንዘብ በህገ ወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ ፖሊስ አሳስቧል፡፡
ጤናማ የንግድ ውድድር እንዳይኖር የሚያደርጉ ግለሰቦች ሲያጋጥሙ ህብረተሰቡ ጥቆማ እና መረጃ በመስጠት ለፀጥታ አካሉ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥልም ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል፡፡
FBC
More Stories
በጥናት ምርምር የተደገፍ ማህበረሰብ ተኮር ተግባራትን ከመፈፀም ባሻገር በጥሩ ስነ ምግባርና እወቀት የታነፁ ትውልድን ከመቅረፅ አኳያ የዩንቨርስቲ መምህራኖች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ።
በሀገሪቱ የኢኮኖሚ ግንባታ ሂደት የነጋዴዉ ማህበረሰብ ሚና ጉልህ መሆኑን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ገለጹ።
በዘንድሮ ዓመት በሚሰጠዉ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና አጠቃላይ ከሚፈተኑ 19ሺህ በላይ ተማሪዎች ዉስጥ ከ2ሺህ 6መቶ በላይ ተማሪዎች በኦንላይን ፈተና እንደሚፈተኑ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ትምህርት ቢሮ አስታወቀ ።