በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተካሄደው ድጋሚ ምርጫ ድምጽ የተሰጠባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ጊዜያዊ ውጤቶችን ይፋ እያደረጉ ነው።
በክልሉ ምሥራቅ ጉራጌ ዞን መስቃን ወረዳ እና በማረቆ ልዩ ወረዳ 6ኛው ሀገራዊ የድጋሚ ምርጫ ላይ ዜጎች በትናንትናው ዕለት ድምጻቸውን መስጠታቸው ይታወሳል፡፡
በምርጫው ሒደት ሲሳተፉ የነበሩ መራጮችም በዛሬው ዕለት የተለጠፈውን ጊዜያዊ ውጤት እየተመለከቱ ይገኛሉ።
የድጋሚ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ በአካባቢዎቹ በሚገኙ በ169 የምርጫ ጣቢያዎች መከናወኑ ይታወቃል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።