የበጀት ዓመቱ የመጨረሻ የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ ባለፉት 10 ወራት ንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና ሳኒቴሽን ዘርፍ የተኛለ ስራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም አሁን ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ72 ሚሊየን ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡“ግድቤን በደጄ” በሚል ፕሮጀክትም በድርቅ የሚጎዱ አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ስራ በስፋት መከናወኑንም ጠቁመዋል፡፡ይህም በቀጣይ በሌሎች አከባቢዎች እንሰዲሰፋ ይሰራል ነው ያሉት፡፡ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ በተለያዩ ተቋማት ሲመሩ የነበሩ የመጠጥ ውሃ ቁፋሮና መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ አግባብ መምራት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት በፍጥነት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡በዚህም ከውሃና ኢነርጂ ዘርፍ በተጨማሪ ከግብርና እንዲሁም ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ያለውን ሃብት በውጤታማነት መጠቀም መቻሉን ገልጸዋል።ለአብነት በተንዳሆ ግድብ ላይ በቅንጅት በተሰራው ህብረተሰቡን የመስኖ ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር በውጤታማነት ጎርፍ የመከላከል ሥራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም መንግስት ያወጣው የነበረውን ተጨማሪ ወጪ ማስቀረት ተችሏል ነው ያሉት፡፡በቀጣይም ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ለኢዜአ ተናግረዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።