የበጀት ዓመቱ የመጨረሻ የ100 ቀናት አፈጻጸም ግምገማ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ተካሂዷል።ሃብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) የውሃና ኢነርጂ ዘርፍ አፈጻጸም አስመልክተው በሰጡት ማብራሪያ÷ ባለፉት 10 ወራት ንጹህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትና ሳኒቴሽን ዘርፍ የተኛለ ስራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም አሁን ላይ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ72 ሚሊየን ዜጎች የንጹህ መጠጥ ውሃን ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ነው የተናገሩት፡፡“ግድቤን በደጄ” በሚል ፕሮጀክትም በድርቅ የሚጎዱ አካባቢዎች የዝናብ ውሃን በማሰባሰብ ተጠቃሚ የሚሆኑበት ስራ በስፋት መከናወኑንም ጠቁመዋል፡፡ይህም በቀጣይ በሌሎች አከባቢዎች እንሰዲሰፋ ይሰራል ነው ያሉት፡፡ከዚህ ቀደም በተበታተነ መልኩ በተለያዩ ተቋማት ሲመሩ የነበሩ የመጠጥ ውሃ ቁፋሮና መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቶችን በተቀናጀ አግባብ መምራት የሚያስችል አሰራር በመዘርጋት በፍጥነት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡በዚህም ከውሃና ኢነርጂ ዘርፍ በተጨማሪ ከግብርና እንዲሁም ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት በመስራት ያለውን ሃብት በውጤታማነት መጠቀም መቻሉን ገልጸዋል።ለአብነት በተንዳሆ ግድብ ላይ በቅንጅት በተሰራው ህብረተሰቡን የመስኖ ተጠቃሚ ከማድረግ ባሻገር በውጤታማነት ጎርፍ የመከላከል ሥራ መከናወኑን አንስተዋል፡፡በዚህም መንግስት ያወጣው የነበረውን ተጨማሪ ወጪ ማስቀረት ተችሏል ነው ያሉት፡፡በቀጣይም ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንደሚሰራ ለኢዜአ ተናግረዋል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ፡- በብዝኃነት ላይ የተመሠረተ ወል ትርክትን የመገንባት ጉዞ
የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ተባለ
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የመደመር መንግስት ያደሩ በርካታ የልማት ጥያቄዎችን ከመፍታት ባሻገር አዳዲሶቹን ጀምሮ በማጠናቀቅ የሕዝቡን ተጠቃሚነት እያረጋገጠ እንደሚገኝ አቶ ፍቅሬ አማን ገለጹ።