ባህላዊ ዕሴቶችን ጠብቆ በማልማትና ለትውልድ ተሻጋሪ ከማድረግ ባሻገር የኢኮኖሚ መሰረት እንዲሆኑ መስራት ይገባል ሲሉ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ም/ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ፡፡
ም/ርዕሰ መስተዳድሩ ለቤንች ብሔረሰብ የዘመን መለወጫ እና የምስጋና በዓል “ቢስት ባር” የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል ።
ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) (ኢ/ር) በመልዕክታቸው ÷የቤንች ብሔረሰብ የራሱ የሆኑ ባህላዊ ዕሴቶች ያሉት መሆኑን አውስተዋል፡፡
እነዚህን ዕሴቶች በመጠበቅ ፣በመንከባከብ ፣በማልማትና ለትውልድ ተሻጋሪ ለማድረግ የቤንች ብሔረሰብ ብርቱ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን ጠቅሰዋል፡፡
የብሔረሰቡ አባቶች ያቆዩትይህ በዓል ለአሁኑ ትውልድ መተላለፉ ትልቅ ሥራ በመሆኑ በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል መስራት ይገባል ብለዋል።
ዕንቁ የሆነውን የቤንች ብሔረሰብ ባህላዊ ዕሴት በመንከባከብ ፣በመጠበቅና በማልማት መልካም ሥራዎች ላይ በማዋል ይበልጥ እየዳበረ እንዲሄድ መስራት እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
ወደ አዲስ ዓመት ሲገባ የተሻለ ለመስራት፣ በውጤት ለመገኘት፣አብሮነትንና አንድነትን ለማጠናከር ሁሉም መዘጋጀት እንዳለበትም ጥሪ አቅርበዋል።
በክልሉ በሚገኙ ብሔረሰቦች በርካታ መልማት የሚገባቸው ባህላዊ ዕሴቶች እንዳሉ ጠቁመው ÷እነዚህን ዕሴቶች በማጥናት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የክልሉ መንግስት አበክሮ ይሰራል ነው ያሉት።
ም/ርዕሰ መስተዳድሩ በዓሉ የሠላም፣ የፍቅር፣የመተሳሰብ ፣የአብሮነት እንዲሆንም መመኘታቸውንም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል።
FBC
More Stories
ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዳያስፖራው ማህበረሰብ አጀንዳ ማሰባሰብ ጀመረ
የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት የዘርፍ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2017 በጀት አመት የአስፈፃሚ አካላት አፈፃፀም ግምገማ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል።
ማህበረሰቡ በከባድ ዝናብ ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች እንዲጠነቀቅ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳሰበ።