የ«ላ ሊና »መከሰት ለወራት የዘለቀውን ሙቀት መጠን ሊቀንስ እንደሚችል መተንበዩን የተመድ የአየር ትንበያ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
ከጎርጎርሳውያኑ 2023 አጋማሽ ጀምሮ ኤል ኒኖ ያስከተለው የዓለም ሙቀት በበርካታ የዓለም አካባቢዎች አስከፊ የአየር ሁኔታ እንደከሰት አድርጓል ያለው ዘገባው የ«ላ ሊና» የዓየር ለውጥን ተከትሎ መቀዛቀዝ እያሳየ መምጣቱን ገልጿል። በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ውስጥም እመርታዊ ለውጥ ሊያሳይ እንደሚችል ዓለማቀፉ ድርጅት ተንብዪዋል።
ትንበያው እንደሚያሳየው ምንም እንኳ በ«በላ ሊና» ክስተት ሙቀቱ በጊዜያዊነት መቀዛቀዝ ቢያሳይም የሰው ልጅ በሚያስከትለው የአየር ንብረት ለውጥ መዘዝ የዓለም ሙቀት እየጨመረ መሄዱ እንደማይቀር ነው። ይህንኑ ተከትሎም የተለያዩ የዓለም አካባቢዎች ወቅቱን ላልጠበቀ ዝናብ እና ሙቀት ሊጋለጡ እንደሚችሉ ነው ዘገባው ያመለከተው።
የውቅያኖስ አካባቢዎችን ሙቀት እንደሚቀንስ ተስፋ የተጣለበት «ላ ኒና » በዋናነት ከነፋስ፣ ከዝናብ እና ከከባቢ አየር ግፊት ለውጥ ጋር ተዳምሮ በሞቃታማው የፓስፊክ ውቅያኖስ አካባቢዎች ውስጥ ያለውን የሙቀት መጠን እንደሚያቀዘቅዝ ይጠበቃል።
የመንግስታቱ ድርጅት ዘገባ እንደሚያመለክተው ላ ሊና ከፊታችን ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉ ወራት የአየር ሁኔታዉን 60 ከመቶ እንዲሁም ከነሐሴ እስከ ህዳር ባሉ ወራት ደግሞ 70 በመቶ የመከሰት ዕድል አለው።
DW
More Stories
በቀጣይ 90 ቀናት የተቀመጡ ዕቅዶችን በውጤታማነት በመፈጸም እመርታዊ ውጤት ለማስመዝገብ ርብርብ ማድረግ ይኖርብናል፦አቶ ፍቅሬ አማን
ምክር ቤቶች የህዝቡ ሁለተናዊ ተጠቃሚነት እንድረጋጥ ድርሻቸው የጎላ በመሆኑ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን ማጠናከር እንደምያስፈልግ ተጠቆመ ።
ኢትዮጵያ ስደተኞችን ተቀብላ በማስተናገድ እያከናወነች ያለው ተግባር የሚደነቅ ነው