የ«ላ ሊና »መከሰት ለወራት የዘለቀውን ሙቀት መጠን ሊቀንስ እንደሚችል መተንበዩን የተመድ የአየር ትንበያ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል።
ከጎርጎርሳውያኑ 2023 አጋማሽ ጀምሮ ኤል ኒኖ ያስከተለው የዓለም ሙቀት በበርካታ የዓለም አካባቢዎች አስከፊ የአየር ሁኔታ እንደከሰት አድርጓል ያለው ዘገባው የ«ላ ሊና» የዓየር ለውጥን ተከትሎ መቀዛቀዝ እያሳየ መምጣቱን ገልጿል። በቀጣዮቹ ጥቂት ወራት ውስጥ ውስጥም እመርታዊ ለውጥ ሊያሳይ እንደሚችል ዓለማቀፉ ድርጅት ተንብዪዋል።
ትንበያው እንደሚያሳየው ምንም እንኳ በ«በላ ሊና» ክስተት ሙቀቱ በጊዜያዊነት መቀዛቀዝ ቢያሳይም የሰው ልጅ በሚያስከትለው የአየር ንብረት ለውጥ መዘዝ የዓለም ሙቀት እየጨመረ መሄዱ እንደማይቀር ነው። ይህንኑ ተከትሎም የተለያዩ የዓለም አካባቢዎች ወቅቱን ላልጠበቀ ዝናብ እና ሙቀት ሊጋለጡ እንደሚችሉ ነው ዘገባው ያመለከተው።
የውቅያኖስ አካባቢዎችን ሙቀት እንደሚቀንስ ተስፋ የተጣለበት «ላ ኒና » በዋናነት ከነፋስ፣ ከዝናብ እና ከከባቢ አየር ግፊት ለውጥ ጋር ተዳምሮ በሞቃታማው የፓስፊክ ውቅያኖስ አካባቢዎች ውስጥ ያለውን የሙቀት መጠን እንደሚያቀዘቅዝ ይጠበቃል።
የመንግስታቱ ድርጅት ዘገባ እንደሚያመለክተው ላ ሊና ከፊታችን ከሐምሌ እስከ መስከረም ባሉ ወራት የአየር ሁኔታዉን 60 ከመቶ እንዲሁም ከነሐሴ እስከ ህዳር ባሉ ወራት ደግሞ 70 በመቶ የመከሰት ዕድል አለው።
DW
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች