የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት ቤት ከጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ዋናው መቀመጫው እና የተመሠረተበት ሀገር ደቡብ ኮሪያ ከሆነው ጉድ ኔበርስ ዓለም አቀፍ በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በጋራ ለመሥራት የሚያስችል ስምምነት መደረሱን የቀዳማዊት እመቤት ጽሕፈት በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈርው መልዕክት አስታውቋል።
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በመልዕክቱ እንደገለጹትም፤ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ ጋር በፅሕፈት ቤታቸው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችን ለመደገፍ እና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አድርገዋል።
በውይይቱም ወደ ስራ የሚያስገባ የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸውን ነው ቀዳማዊት እመቤቷ የጠቀሱት፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች