May 20, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አርሰናል የፕሪምየር ሊግ ዋንጫ ከ22 ዓመት በኋላ ማሸነፉን አረጋግጧል።

ግንቦት 11/2018 ዓ.ም

አርሰናል ተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ ከ22 ዓመት በኋላ የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫ ማሸነፉን አረጋግጧል።

ማንችስተር ሲቲ በ37ኛ ሳምንት የሊግ መርሐግብሩ ከቦርንማውዝ ጋር 1ለ1 ተለያይቷል። በቪታሊቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ ለቦርንማውዝ ፣ ኧርሊንግ ሃላንድ ለሲቲ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ሲቲ ከመሪው አርሰናል ያለው ልዩነት አራት ነጥብ ሆኗል። ይህም አርሰናል አንድ ቀሪ ጨዋታ እያለው የሊጉ አሸናፊ እንዲሆን አስችሎታል።