May 18, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የፕሬዝዳንቶቹ የስልክ ውይይት

ማሻ ፣ የግንቦት 10፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም)ፕሬዝዳንት ትራምፕ እና ፕሬዝዳንት ፑቲን በስልክ ለመመከር ቀጠሮ መያዛቸውን ከክሬምሊን የወጡ መረጃዎች አመላክተዋል::

የኢስታንቡል የሰላም ውይይትን ተከትሎ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ለመምከር ቀጥሮ መያዛቸውን በትሩዝ ማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል::

የሁለቱ መሪዎች የስልክ ውይይት ለነገ ሰኞ ቀጠሮ የተያዘለት ስለመሆኑ ክሬምሊን አረጋግጧል::

የመሪዎቹ ውይይት የሩስያ ዩክሬን ጦርነት እንዲያበቃ በሚያስችል ጉዳይ ላይ እንደሚሆን ይጠበቃል::

የሁለቱ ሀገራት የንግድ ጉዳይ በፕሬዝዳንቶቹ የስልክ ውይይት ላይ የሚነሳ ሌላው አጀንዳ እንደሚሆንም ይጠበቃል::

ፕሬዝዳንት ትራምፕ “የሩስያ ዩክሬንን ሰላም ማምጣት የምችለው እኔ ነኝ” ማለታቸው የሚታወስ ነው ሲል ቲአርቲ ዘግቧል::