ማሻ ፣ የግንቦት 05፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት አራት ቀናት የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ የሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸውን የመጀመሪያ የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸውን በሳዑዲ አረቢያ ጀምረዋል።
ዛሬ ሪያድ የገቡት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት ዋነኛ ዓላማ ለአሜሪካ ኢኮኖሚ ትልቅ አዲስ ኢንቨስትመንትን ለማስፈን ያለመ ስለመሆኑ ተዘግቧል፡፡
በሳውዲ አረቢያ ቆይታቸው የሳውዲ-አሜሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የሚሳተፉት ፕሬዚዳንት ትራምፕ፤ ጉብኝታቸው በመጪው አርብ የሚጠናቀቅ መሆኑ ተመላክቷል።
Fana
More Stories
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች
ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው
ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ የጠፈር ጣቢያዋን ለውጭ ሀገር ጠፈርተኞች ክፍት አደረገች