ማሻ፣ ጥር 03/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍኤም 103.8) አሜሪካ በሶሪያ በሚገኘው እስላማዊ መንግስት ብላ በምትጠራው ላይ ከባድ ጥቃት ፈፀመች ተባለ።
ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው ወር በሶሪያ ፓልሜራ በአሜሪካ ወታደሮች ላይ ለደረሰው ጉዳት የበቀል ምላሽ ነው ስትል ዋሽንግተን አስታውቃለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ እንዳስታወቀው ፣ አይ አይ ኤስ ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት አድርሷል።
ዘመቻ ሀውክአይ በተሰኘው ትራምፕ መራሽ ጥቃት አይ ኤስ ሲጠቀምበት የነበረው የጦር መሳሪያ መውደሙን ማዕከላዊ ዕዙ አክሎ ገልጿል።
አይ ኤስ ላይ የተወሰደው እርምጃ ለወደፊቱ ቡድኑ ለሚያደርገው ጥቃት ከባድ አጸፋ እንደሚጠብቀው ለማስጠንቀቅ ነው ሲሉ የዋሽንግተን ባለስልጣናት ተናግረዋል።
በአሜሪካ ጦር እና ተባባሪዎች ላይ የሚደርስ ጥቃት መልሱ የከፋ መሆኑን አይ ኤስ እና ሌሎች ቡድኖች ማወቅ አለባቸው ሲል ማዕከላዊ ዕዙ በኤክስ ገፁ ላይም አስፍራሯል ሲል ታይምስ ኦፍ ኢንዲያን ጠቅሶ ኤን ቢሲ ኢትዮጵያ ዘግቧል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች