ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ‘ኢቴኤክስ 2025’ ከዛሬ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ፤ የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ፋይን ቴክ፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርትን መሰረት ያደረገ አምስት የትኩረት መስኮችን የያዘ ነው ተብሏል።
በቴክኖሎጂው ዘርፍ እንደ ሀገር የተሠሩ ስራዎችን ለዓለም ለማሳየት እና በቀጣይ መሰራት የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ አቅምን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።
የሦስት ቀናት ቆይታ በሚኖረው ኤክስፖው ላይ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ሮቦቲክስ ውድድሮች፣ ዐውደ ርዕዮች እንዲሁም ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ አቅምን የሚፈጥሩ በርካታ የጎንዮሽ ውይይቶች እንደሚደረጉም ተመላክቷል።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚካሄደው ኤክስፖ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች እንደሚሳተፉም ተገልጿል።
ፋና
More Stories
ቲክቶክ በአውሮፓ ክስ ቀረበበት
የዜጎችን ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ለማሳደግ በነጻ የቀረበው የኮደርስ ስልጠና
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከ“ቴክ ቶክ ከሰለሞን ጋር” በክፍል አንድ በነበራቸው ቆይታ ካነሷቸው በርካታ ጉዳዮች መካከል፡-