ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ‘ኢቴኤክስ 2025’ ከዛሬ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ፤ የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ፋይን ቴክ፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርትን መሰረት ያደረገ አምስት የትኩረት መስኮችን የያዘ ነው ተብሏል።
በቴክኖሎጂው ዘርፍ እንደ ሀገር የተሠሩ ስራዎችን ለዓለም ለማሳየት እና በቀጣይ መሰራት የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ አቅምን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።
የሦስት ቀናት ቆይታ በሚኖረው ኤክስፖው ላይ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ሮቦቲክስ ውድድሮች፣ ዐውደ ርዕዮች እንዲሁም ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ አቅምን የሚፈጥሩ በርካታ የጎንዮሽ ውይይቶች እንደሚደረጉም ተመላክቷል።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚካሄደው ኤክስፖ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች እንደሚሳተፉም ተገልጿል።
ፋና
More Stories
የማህበራዊ ሚዲያው ተፅዕኖ የጎላበት ምህዳር ተፈጥሯል- የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ።
የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች ተልዕኮቸውን በሀላፍነት እና በዕውቀት እንዲወጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ።
የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ በድህረገጽና በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።