ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ‘ኢቴኤክስ 2025’ ከዛሬ ግንቦት 8 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እና የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት በጋራ ያዘጋጁት ይህ ኤክስፖ፤ የሳይበር ደህንነት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ፋይን ቴክ፣ ስማርት ሲቲ እና የቴክኖሎጂ ትምህርትን መሰረት ያደረገ አምስት የትኩረት መስኮችን የያዘ ነው ተብሏል።
በቴክኖሎጂው ዘርፍ እንደ ሀገር የተሠሩ ስራዎችን ለዓለም ለማሳየት እና በቀጣይ መሰራት የሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ተጨማሪ አቅምን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነም ተገልጿል።
የሦስት ቀናት ቆይታ በሚኖረው ኤክስፖው ላይ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ እና ሮቦቲክስ ውድድሮች፣ ዐውደ ርዕዮች እንዲሁም ከኢትዮጵያ አልፎ ለአፍሪካ አቅምን የሚፈጥሩ በርካታ የጎንዮሽ ውይይቶች እንደሚደረጉም ተመላክቷል።
ከግንቦት 8 እስከ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በሚካሄደው ኤክስፖ ከ10 ሺህ በላይ ታዳሚዎች እንደሚሳተፉም ተገልጿል።
ፋና
More Stories
በቻይና የተሰራው የዓለማችን ግዙፉ የጭነት ድሮን
በፀሐይ ኃይል የሚሠራው አነስተኛ ትራክተር ለማላዊ አርሶ አደሮች አዲስ ተስፋን ይዞ መጥቷል
የነዳጅ ዘመን እያበቃ ይሆን? በ2030 የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር ነው