ማሻ ፣ የግንቦት 09፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ “አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስን ለአፍሪካ ብልጽግና እና ትብብር” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ባለው “አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ለአፍሪካ” መርሃ ግብር ላይ፥ አፍሪካ በሀገር በቀል የአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ የተመራ አካታች ብልጽግና በማምጣት የአጀንዳ 2063 ግቦችን ለማሳካት ወደ አዲስ ዘመን እየተሻገረች መሆኑን አጽንኦት ሰጥተው አንሰተዋል።
ኢትዮጵያም በአርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ፣ በዲጂታል መሠረተ ልማት እና የክሂሎት ማበልጸጊያ ሥራዎች በአርዓያነት እየመራች መሆኑን አውስተዋል።
እንደ ኢትዮጵያ አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስ ኢንስቲቲዮት፣ ዲጂታል መታወቂያ ብሎም “የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ” ባሉ ፕሮግራሞቿ ኢትዮጵያ ሕልሞቿን ወደ ተጨባጭ ተፅዕኖ ፈጣሪ ተግባራት መለወጥ ችላለች።
በ2030 ማንም ወደ ኋላ በማይቀርበት አኳኋን አፍሪካ አርቴፊሻል ኢንተሊጀንስን በራሷ መልክ በሥነምግባር፣ በአካታችነት እና ዘላቂነት ቅርፅ ማስያዝ እንደሚኖርባት ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስምረውበታል።
More Stories
በቻይና የተሰራው የዓለማችን ግዙፉ የጭነት ድሮን
በፀሐይ ኃይል የሚሠራው አነስተኛ ትራክተር ለማላዊ አርሶ አደሮች አዲስ ተስፋን ይዞ መጥቷል
የነዳጅ ዘመን እያበቃ ይሆን? በ2030 የታዳሽ ኃይል አጠቃቀም በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር ነው