ቻይና በጠፈር ምርምር ታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸውን ጠፈርተኞች ወደ “ቲያንጎንግ” የጠፈር ጣቢያዋ ልትልክ መሆኑን አስታውቃለች።
“ቲያንጎንግ” ወይም “የሰማይ ቤተመንግስት” ተብሎ የሚጠራው ይህ ግዙፍ የሳይንስ ላብራቶሪ፣ እስካሁን ለቻይናውያን ጠፈርተኞች ብቻ ሲያገለግል የቆየ ቢሆንም፣ አሁን ግን የፓኪስታን ተወላጅ ለሆኑት ሙሐመድ ዚሻን አሊ እና ኩራም ዳውድ በሩን ክፍት አድርጓል።
እነዚህ ሁለት ጠፈርተኞች በቅርቡ ወደ ቻይና በመጓዝ በጠፈር ጣቢያው ውስጥ ለሚኖራቸው ቆይታ የሚያግዛቸውንና ከባድ የተባለውን የተግባር ስልጠና ይጀምራሉ።
ይህ ታሪካዊ ውሳኔ ቻይና በጠፈር ምርምር መስክ ያላትን የቴክኖሎጂ ልዕልና ለሌሎች ሀገራትም ለማጋራትና የዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ ነው።
በተለይም እንደ ፓኪስታን በዘርፉ ላይ በትጋት እየሰሩ ላሉ ሀገራት፣ ይህ ጉዞ እጅግ ዘመናዊ ከሆነው የቻይና የጠፈር ቴክኖሎጂ ጋር በቀጥታ እንዲተዋወቁና ትልቅ ልምድ እንዲቀስሙ ሰፊ እድል ይከፍትላቸዋል።
እንደ ሲጂቲኤን ዘገባ ከሆነ፣ ይህ እርምጃ ከሳይንሳዊ ትብብር ባለፈ በቻይና እና በፓኪስታን መካከል ያለውን ስትራቴጂካዊ ግንኙነት ወደ ላቀ የቴክኖሎጂ እና የሳይንስ ከፍታ የሚያሸጋግር ነው።
ቻይና የጠፈር ጣቢያዋን ለሌሎች ሀገራት ክፍት ማድረጓ ወደፊት በርካታ ሀገራት በጋራ የሚሰሩበት ዓለም አቀፋዊ የጠፈር ምርምር ማዕከል የመሆን ተስፋውን ይበልጥ እንዲያብብ አድርጎታል።
More Stories
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ኅብረት የሰው ሠራሽ አስተውሎት እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ ሆነው በአፍሪካ ኅብረት ጉባኤ ተሾሙ
ኢትዮጵያ ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የሚላመድና የማይበገር የልማት ግስጋሴዋን በተጨባጭ ውጤቶች እያስመሰከረች ቀጥላለች።
በማህበራዊ ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋጡ የልማት ስራዎች ተሰርተዋል፦ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ