ማሻ ፣ የሚያዝያ 26፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) በምረቃው ፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ በከተማው የተገነባው ይህ ጤና ጣቢያ የአካባቢው ማህበረሰብ የጤና አገልግሎት ፍላጎትን ከማሟላት ረገድ ሚናው የጎላ ስለመሆኑ ተናግረዋል።
አምራችና ሀገር ተረካቢ ትውልድ ለመፍጠር እንደ ሀገር የተያዘውን ህልም እውን ለማድረግ የጤናው ዘርፍ ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀው ይህንንም ከማረጋገጥ አኳያ የመንግስት ብቻ ሳይሆን የግሉንም ተቋም ደረጃ ከፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።
እንደዚህ አይነት ትላልቅ ኢንቨስትመንት አስፈላጊ መሆኑን መንግስታችን ስለሚያምን በሁሉም ዘርፍ ለመሰማራት የሚፈልጉ አልሚ ባለሀብቶች በዞኑ መጥተው እንዲያለሙና መንግስትም ተገቢውን ድጋፍ በተጠየቀው ሁሉ ያደርጋል ለዚህም በሁሉም የዞኑ የመንግስት መዋቅር በተቀናጀ መልኩ ይሰራል ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።
የሸካ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ እምሩ ወዬሳ በመድረኩ ባስተላለፉት መልዕክት ተቋሙን በመደገፍና አስፈላጊውን ስልጠናና ክትትል ከማድረግ አንፃር በትኩረት እንደሚሠራ ገልፀው ከመንግስት ተቋማት ጋር የማስተሳሰር ስራ እንደሚሰራም ተናግረዋል።
የቴፒ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ባስተላለፉት መልዕክት የከተማውን ህብረተሰብ የጤና አገልግሎት አቅርቦት ደረጃ ከፍ የሚያደርግ ተቋም እንደሚሆንና ከተማዋ በሚታደርገው የደረጃ ለውጥ ስራ በማህበራዊ ዘርፍ መስፈርት ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት አስታውሰዋል።
የጤና ጣቢያው ባለቤት ይታያል ተካ ተቋሙን ሲያስጎበኙ እንደተናገሩት በአጠቃላይ ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተገነባና ከ25 በላይ የሚሆኑ ሠራተኞች በስሩ እንዳሉት ተናግረው ከአገልግሎት አንፃርም ቀላል ምርመራ፣የእናቶችና ህፃናት ጤና እንክብካቤ፣ ቅድመና ድህረ ወሊድ ክትትል፣የማዋለድ አገልግሎት፣የቀዶ ህክምናን ጨምሮ ሁሉንም ምርመራና ህክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
በቀጣይም አገልግሎቱን በማስፋትና በማሳደግ ወደ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማሳደግ እቅድ እንዳላቸው የጠቆሙት ባለሃብቱ አስፈላጊውን ድጋፍ መንግስት እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች