ማሻ ፣ የሚያዝያ 19፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የኢራን ቁልፍ ወደብ በሆነው ሻሂድ ራጃኢ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ 800 የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል።
በፍንዳታው 6 ሰዎች የደረሱበት አለመታወቁም ነው የተጠቆመው።
አደጋው ከተነሳበት ስፍራ እስከ 50 ኪሎ ሜትር ርቀት ድረስ ያሉ ተሽከርካሪዎች እና ህንፃዎች ላይ ጉዳት ማድረሱ ነው የተጠቆመው።
“ፍንዳታው ለኢራን ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ጥቅም ላይ እንዲውል የታሰበው የሶዲየም ሮኬት ነዳጅ ወይም ሶዲየም ፐርክሎሬት የሚባለው ኬሚካል በትክክል ባለመጫኑ ሳቢያ የተከሰ ነው” ሲል የዓለም የባህር ስጋት አስተዳደር ድርጅት አምበሪ ኢንተለጀንስ አስታውቋል።
አምበሪ ኢንተለጀንስ ከዚህ ቀደም በሻሂድ ራጃኢ ያለውን አግባብነት የጎደለው የኬሚካል አቀማመጥን በተመለከተ ማስጠንቀቂያን ሰጥቶ እንደነበርም አስታውሷል።
ጭነቱን በተመለከተ የፋይናንሺያል ታይምስ ጋዜጣ ሁለት የሶዲየም ሮኬት ነዳጅ የጫኑ መርከቦች ከቻይና ወደ ኢራን መግባታቸውን አመላክቶ ነበር።
አደጋውን ተከትሎ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን በአደጋው ለተጎዱ እና ህይወታቸው ላለፈ ወገኖች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።
በዚህም ፍንዳታው የተከሰተው የእሳት ቃጠሎ ከተነሳ በኋላ ተቀጣጣይ ቁሶችን በውስጣቸው በያዙ እና ያልተዘጉ ወደ ነበሩ ኮንቴነሮች መዛመቱን ተከትሎ መሆኑን ጠቅሷል።
አሜሪካ ኢራን የራሷን የኒኩሌር ኃይል እንዳታበለፅግ ለማድረግ ውይይቶችን እያካሄደች ባለበት ወቅት የተከሰተው አደጋው ሀገራቱን ውጥረት ውስጥ የሚያስገባ ሊሆን ይችላል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።
ኢቢሲ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች