ማሻ ፣ የመጋቢት 29፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የፓስፖርት አገልግሎት ደንበኞችን በማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ከአገልግሎቱ የተገኘው መረጃ እንዳመለከተው ተጠርጣሪዎቹ አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን የሚል ማታለያ በመጠቀም በ24 የአገልግሎቱ ደንበኞች ላይ የማጭበርበር ወንጀል መፈጸማቸው ተጠቅሷል፡፡
የወንጀል ድርጊቱን ፈፅመዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ተቋሙ ለ5 ቀን 20 ሺህ ብር የሚያስከፍለውን 28 ሺህ ብር ሲያስከፍሉ መቆየታቸውም ነው የተገለፀው፡፡
አገልግሎቱ ከፌደራል ፓሊስ እና ከአዲስ አበባ ፖሊስ ጋር በቅንጅት ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው፣ ተገልጋዮቹ የከፈሉት ገንዘብ እንዲመለስ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
ደንበኞች ከመሰል የማጭበርበር ተግባር ራሳቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም ስለአገልግሎቱ ማንኛውም አይነት መረጃ ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የመረጃ ዴስክ አልያም ከተቋሙ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንዲያገኙ አገልግሎቱ አሳስቧል፡፡
ኢቢሲ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች