በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ ዕዳ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ከታክስ ዕዳ 41 ቢሊየን 662 ሚሊየን 896 ሺህ 213 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 49 ቢሊየን 664 ሚሊየን 299 ሺህ 370 ብር መሰብሰቡን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡
ከፍተኛ የታክስ ዕዳ መጠን ያለባቸውን ታክስ ከፋዮች በመለየት ቅድሚያ ተሰጥቶ መሠራቱና ለዋና መስሪያ ቤት በልዩ ሁኔታ እንዲታዩ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ፈጥኖ ምላሽ መስጠቱ ለዕቅዱ መሳካት ማገዙ ተገልጿል፡፡
ከተሰበሰበው የታክስ ዕዳ ውስጥ 30 ቢሊየኑ 30 ቀን ካልሞላው የታክስ ዕዳ መሰብሰቡን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች