ኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለመከላከል በሰራችው ውጤታማ ሥራ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ሥነ ሕዝብ ድርጅት እውቅና አገኘች።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በትናንትናው እለት በኒውዮርክ የተመድ ዋና መስሪያ ቤት ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡
ሚኒስትሯ የኢትዮጵያ መንግስት በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችና ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ለማስወገድ የወሰዳቸውን የህግ፣ የፖሊሲና የፕሮግራም እርምጃዎች አብራርተዋል።
እውቅናና ሽልማቱ መንግስት ለስርዓተ ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት ያለውን ቁርጠኝነት የበለጠ የሚያጠናክር እንደሆነም ገልፀዋል፡፡
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የተመድ ምክትል ዋና ፀሐፊ አሚና መሃመድ፣ የተመድ ሥነ ህዝብ ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ናታኒያ ካኔምና ሌሎች የተመድ አባል ሀገራትና የዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ያለ እድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስወገድ የተቋቋመው ጥምረት በፈረንጆቹ 2012 የተመሰረተ ሲሆን÷ በጥምረቱ ውስጥ የመንግስት ተቋማት፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የምርምር ተቋማትና የሃይማኖት ተቋማት ይገኛሉ፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች