
የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ልብስ ለብሰው ግን ደግሞ ሆዳቸው ባዶ የሆኑ አቅም ያጠራቸውን ወገኖቻችን በየአካባቢያችን ልናስባቸው ይገባል ሲሉ ተናገሩ፡፡የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተስፋ ብርሃን የምገባ ማዕከል ቁጥር 4 በመገኘትለአቅመ ደካሞች ማዕድ አጋርተዋል፡፡ሚኒስትሩ አለሙ ስሜ (ዶ/ር) በዚህ ወቅት ÷ መሰል ተግባር በምናምነው ሃይማኖት፣ በመንፈሳዊ እና በዓለማዊውም የሚደገፍ ተግባር መሆኑን ጠቅሰው አቅም ካጠራቸው ጋር ያለንን ማካፈል ከተረፈው ብቻ ሳይሆን ካለው የሚደረግ ተግባር እንደሆነም አንስተዋል።ይህንን የመሰለውን ለአቅመ ደካሞች ማዕድ የማጋርት በጎ ተግባር እየደገፉ ያሉ ተቋማት እና አካላት ሊመሰገኑ እንደሚገባ ደግሞ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናግረዋል።
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች