ማሻ ፣ የግንቦት 08፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የማህበራዊ ሚዲያ መተግበሪያው ቲክቶክ የአውሮፓ ህብረትን የዲጂታል አገልግሎት ሕግ ጥሷል በሚል ክስ ቀርቦበታል።
በዚህ ክስ የቲክቶክ ባለቤት ባይትዳንስ ከዓለም አቀፍ ገቢው እስከ 6 በመቶ የሚደርስ ቅጣት ሊጣልበት ይችላል ተብሏል።
የአውሮፓ ህብረት ሥራ አስፈፃሚ፥ ቲክቶክ ተጠቃሚዎቹ የማጭበርበሪያ ማስታወቂያዎችን ለይተው እንዲያውቁ የሚያስችላቸውን የዲጂታል አገልግሎት ሕግ ማክበር አልቻለም ብሏል።
በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ቲክቶክ ለማስታወቂያ ለማን እንደሚከፍል፣ ማስታወቂያው ማን ላይ እንደሚያነጣጥር እና ማስታወቂያዎቹ ምን እንደያዙ በግልፅ እያሳየ አለመሆኑን ገልጿል።
በሌላ በኩል ክስ የቀረበበት ቲክቶክ የአውሮፓ ህብረት የዲጂታል አገልግሎት ሕግን የተረዳበትን መንገድ አልደግፍም ሲል ተቃውሟል።
ቲክቶክ መተግበሪያውን ይበልጥ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ግልፅ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አሳውቋል::
የማስታወቂያ አሠራሩን ለሕዝብ ክፍት ለማድረግም በንቃት እየሰራ መሆኑን ገልጿል።
ኢቢሲ
More Stories
የማህበራዊ ሚዲያው ተፅዕኖ የጎላበት ምህዳር ተፈጥሯል- የክልሉ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ የሺዋስ አለሙ።
የሚዲያና ኮሚኒኬሽን ባለሙያዎች ተልዕኮቸውን በሀላፍነት እና በዕውቀት እንዲወጡ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድሩ ዶክተር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ አሳሰቡ።
የደቡብ ምዕራብ ሚዲያ ኔትወርክ በድህረገጽና በማህበራዊ ሚዲያ ዘርፍ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በታርጫ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።