ዴንማርክ በአርክቲክ እና በሰሜን አትላንቲክ በረጅም ርቀት ድኖን የሚደረገውን የቅኝት እና የስለላ ስራ ለማጠናከር 400 ሚሊዮን ዶላር መድባለች ተብሏል
እንደዘገባው ከሆነ መንግስት በምዕራብ ግሪንላንድ የሚገኘውን የቀድሞ የአሜሪካ የጦር ሰፈር የነበረውን ኤየርፖርት ኤፍ-35 ጄቶችን እንዲይዝ ለማደስም አስቧል።
ዴንማርክ በአርክቲክ እና በሰሜን አትላንቲክ በረጅም ርቀት ድኖን የሚደረገውን የቅኝት እና የስለላ ስራ ለማጠናከር 400 ሚሊዮን ዶላር መድባለች ተብሏል።
ትራምፕ በከፊል ራስ ገዝ የሆነችውን የዴንማርኳን የአርክቲክ ግዛት ግሪንላንድን ለመያዝ ያላቸውን ፍላጎት በድጋሚ በዚህ ሳምንት ገልጸዋል። የግሪንላንድ መከላከያ እና ጸጥታ ሁኔታዎች የምትቆጣጠረው ዴንማርክ በሰፊዋ ደሴት ያላት ወታደራዊ አቅም ውስን ነው።
በአሁኑ ወቅት አራት ያረጁ የቁጥጥር መርከቦች፣ አንድ የቅኝት አውሮፕላን እና 12 ዶግስሌጂ ቃኝዎች ያሉ ሲሆን የፈረንሳይን አራት እጥፍ የምታክለውን ደሴት እንዲቆጣጠሩ ተመድበዋል።
ዴንማርክ የመከላከያ በጀቷን በእጁጉ ከቀነሰች ከእስር አመታት በላይ በኋላ ባለፈው አመት ለ 10 አመታት የሚያገለግል የ 26 ቢሊዮን ዶላር የመደበች ሲሆን ከዚህ ውስጥ የተወሰነው ለአርክቲክ የሚውል ነው።
ባለፈው ሳምንት የዴንማርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ላርስ ሎክ ራስሙሰን ዴንማርክ ግዙፍ ወታደራዊ ግንባታ እያደረገች መሆኑን ለትራምፕ ለማሳወቅ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል። ነገርግን የመከላከያ ሚኒስትሩ ትሮልስ ለንድ አስፈላጊ ወታደራዊ ኢንቨስትመንቶች ለበርካታ አመታት ችላ ተብለው መቆየታቸውን በትናንትናው እለት ገልጸዋል።
ዴንማርክ በግሪንላንድ የምታደርገው ወታደራዊ ግንባታ የአሜሪካን ስጋት የሚቀርፍ እንዲሆን ይደረጋል የሚል አቋም እያራመደች ነው።
አሜሪካ አሁንም በሰሜንምዕራብ ግሪንላንድ ፒቱፊክ ወታደራዊ ይዞታ አላት።
ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከግሪንላንድ በተጨማሪ የፓናማ ቦይን እንደሚጠቀልሉ እንዲሁም ካናዳ የአሜሪካ 51 ግዛት እንድትሆን እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
More Stories
የአየር ጠባይ ትንበያ መረጃ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የውኃ ሙሌት በታቀደው መሠረት እንዲከናወን ድርሻውን ተውጥቷል – ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ(ዶ/ር)
መጪው የበጋ የአየር ጠባይ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ በሚኖርባቸው አካባቢዎች በደረሱ ሰብሎች ላይ ተጽዕኖ ሊያደርስ ይችላል ተባለ።
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።