ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን ጥረት እያስተጓጎለ ያለው ከፍተኛ ነፋስም እሳቱ እንዲዛመትና እንዲስፋፋ እያደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በዚህም ሰደድ እሳቱ ከሆሊውድ መንደሯ ሎስ አንጀለስ አልፎ ወደ ሌሎች አካባቢዎች የመዛመት ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡
እሳቱን ለማጥፋት በሚደረገው ርብርብም ከመደበኛ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች በተጨማሪ 1 ሺህ የሚጠጉ የሕግ ታራሚዎች እየተሳተፉ መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ታራሚዎቹ እያደረጉት ላለው አስተዋጽኦ ክፍያ እንደሚፈጸምላቸው እና ይህም በካሊፎርኒያ የእርምት እና የመልሶ ማቋቋም መምሪያ (ሲሲአር) የሚመራ የረዥም ጊዜ የበጎ ፈቃድ መርሐ-ግብር አካል መሆኑን ዘገባው አመላክቷል፡፡
እስከ አሁን ከ10 ሺህ በላይ ሕንጻዎችን ያወደመው ሰደድ እሳቱ÷ በ37 ሺህ ሔክታር ላይም ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል፡፡
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች