በሸካ ዞን በሁሉም መዋቅሮች የፓርቲና የመንግስት ሥራዎች አፈጻጸም የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ እየተገመገመ ይገኛል።
የፓርቲና የመንግስት ኢንሼቲቮችን በበላይነት በመምራትና ውጤታማነታቸው ይበልጥ ተጠናክሮ እንዲቀጥሉ አመራሩ በባለቤትነት በመምራት የህዝብ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንዲያስችል የጋራ መግባባት ላይ እንዲደረስ ያለመ የውይይት መድረክ እንደሆነም ተጠቁሟል።
በወረዳና በከተማ አስተዳደር የተደረጉ የአመራር ግምገማና ምዘና አፈጻጸም እየተገመገመ ይገኛል።
የአመራር ምዘናው ጠንካራ ተቋም በመገንባት የህዝብ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚረዳና አሰራሮችን በመትከልና የፓርቲውን ተልዕኮዎች በብቃት በመፈጸም ውጤታማ አሰራር እንዲኖር ማስቻል ዓላማው እንደሆነም ተገልጿል።
በውይይቱ አመራሩ ለቀጣይ ተልእኮ ራሱን የሚያዘጋጅ እና ለህዝቡ የላቀ ተጠቃሚነት ተግባራትን የሚመራበት አቅጣጫም የሚቀመጥ ይሆናል።
በመድረኩ የክልል ደጋፊ አመራሮች፣የዞን ማዕከል አጠቃላይ አመራሮችና የወረዳ/ከተማ አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት እየተሳተፉ ይገኛሉ ሲል የዞኑ መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች