ማሻ፤ መጋቢት 8/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ምክር ቤቱ 4ኛ ዓመት 6ኛ መደበኛ ጉባኤውን በዞኑ ቴፒ ከተማ ላይ እንደሚያካሄድ የምክር ቤቱ ዋና አፈጉባኤ አቶ ጌታቸው ኬኒ ገልፀዋል።
በክልሉ በ2018 በጀት ዓመት ስድስት ወራት ፀጥታን የማስጠበቅ ፣ የዝርፊያና የስርቆት ወንጀሎችን መከላከል እንዲሁም ከወሰን ጉዳዮች ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ የማድረግ ስራዎች ላይ ምክር ቤቱ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።
ነገ በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ በ2018 ዓ.ም 6 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ተግባራት ሪፓርት ቀርቦ ውይይቶች እንደሚደረጉ ዋና አፈጉባኤው በመግለጫቸው ጠቁመዋል ።
በጉባኤው ላይ የክልሉ መንግሥት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ፣ የሁሉም ብሔረሰብ ተወካዮች እና የተለያዩ ተጋባዥ እንግዶች ይሳተፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅም ምክር ቤቱ አስታውቋል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች