ማሻ፤ የካቲት 24/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) እስራኤል በኢራን ፕሬዝዳንታዊ ቢሮ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መሰንዘሯን አስታውቃለች፡፡
ተባብሶ በቀጠለው በዚህ ጥቃት ቴህራንን ጨምሮ በርካታ የኢራን ግዛቶች መትቻለሁ ብላለች እስራኤል፡፡
ቢቢሲ በበኩሉ ናታንዝ የተሰኘው የኢራን የኒኩሌር ጣቢያ መውደሙን አረጋገግጫለሁ ብሏል፡፡
በሌላ በኩል የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር ቴላቪቭ ተጨማሪ ጥቃቶችን ለመሰንዘር በሊባኖስ ቁልፍ ስፍራዎችን እየያዘች እንደምትገኝ ተናግረዋል፡፡
ኢራን በበኩሏ የመልስ ምት የሚሆኑ በርካታ ጥቃቶችን መሰንዘሯን ስትቀጥል፤ 30 የሚሆኑ የጦር ሰፈሮችን ዒላማ አድርጊያለሁ ብላለች፡፡
በሪያድ ሳውዲ የሚገኘው የአሜሪካ ኢምባሲ በኢራን ሁለት ድሮኖች በደረሰበት ጥቃት መውደሙም ተነግሯል፡፡
እስራኤልና አሜሪካ በኢራን እስካሁን ባደረሱት ጥቃት የሟች ቁጥር ወደ 787 ከፍ ብሏል፡፡
በኩዌት ስድስት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውም ታውቋል፡፡
የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት በፈጠረው ቀውስ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዘይት ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን የቢቢሲ ዘገባ አመላክቷል፡፡
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች