ማሻ፣ ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ልዑክ በሸካ ዞን ቴፒ ከተማ እየተገነባ የሚገኘው የክልል ቢሮ ግንባታ ያለበትን ደረጃ ምልከታ አደረገ።
የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎቹ በዞኑ ቴፒ ከተማ በግል ባለሀብቱ ኢንጅነር ታደሰ አድማሱ በዘመናዊ መልክ የሚተከል የቡና ማሳንም ጉብኝተዋል ።
የቡና ማሳው በተለያዩ ዓይነት ቴክኖሎጂዎች ተደግፎ የሚለማ ሲሆን አሠራሩም የቡና ጥራትን በማስጠበቅ ተወዳዳሪ የሆነውን ቡና ለዓለም ገቢያ በብዛት እንዲቀርብ የሚያስችል ነው ተብሏል ።
በጉብኝቱ ላይ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ኢንጂነር ነጋሽ ዋገሾን ጨምሮ የክልል፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች