ማሻ፣ ታህሳስ 19/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ ሁለተኛ ዙር የመጀመሪያ ጨዋታ ሞዛንቦክ ጋቦንን 3 ለ 2 አሸንፋለች።
በሞሮኮ አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ቀን 9፡30 ላይ በተደረገው ጨዋታ የሞዛንቢክን ግቦች ዲዮጎ ካሊላ፣ ጄኒ ካታሞ፣ ፋይሳል ባንጋል ሲያስቆጥሩ÷ ኦባሚያንግ እና ሙኬቱ ሙሳውንዳ የጋቦንን ግቦች አስቆጥረዋል።
የዛሬው መርሐ ግብር ጨዋታዎች ቀጥለው ሲካሄዱ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢኳቶሪያል ጊኒ ከሱዳን እንዲሁም ምሽት 2:30 ላይ አልጄሪያ ከቡርኪናፋሶ፤ ምሽት 5 ሰዓት ኮቲዲቯር ከካሜሩን ይገናኛሉ።
More Stories
አርሰናል ከ20 ዓመት በኋላ በሻምፒዮንስ ሊግ ለፍጻሜ ደረሰ
ማንቼስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን በማሸነፍ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎውን አረጋገጠ
ኬንያዊው አትሌት በሽልማት ተንበሸበሸ