አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 11፣ 2018 (ማሻ ኤፍኤም 103.8) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የታለመለትን ግብ አሳክቶ ተጠናቋል አሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዛሬው እለት ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030ን በይፋ አስጀምረዋል፡፡
ተደራሽነትን ማስፋት፣ ለዜጎች እኩል እድል መፍጠር እንዲሁም በዜጎችና ተቋማት መካከል መተማመንን ማጎልበት ደግሞ የስትራቴጂው ቁልፍ መሰረታዊ ትልሞች መሆናቸው አመልክተዋል፡፡
እነዚህ ትልሞች እንዲሳኩ በተለይ የህዝብ ዲጂታል መሠረተ ልማትን ማስፋት ላይ ትልቅ ስራ እንደሚከናወን ገልጸው፥ ይህም ዲጂታል ቴክኖሎጂ ሰው ተኮር ሆኖ የዜጎችን ኑሮ እንዲያሻሽል ትልቅ አቅም ይፈጥራል ነው ያሉት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ በአጠቃላይ በዲጂታል ኢትዮጵያ የሚከናወኑ ስራዎች የመደመር መንግስት በቀለለ ቢሮክራሲ ታላላቅ ስትራቴጂዎችን እውን ለማድረግ ከያዘው ግብ ጋር የተሳሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።
#(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
በማህበራዊ ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋጡ የልማት ስራዎች ተሰርተዋል፦ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ
በክልሉ በኢኮኖሚ ፤በመሰረተ ልማት፤በማህበራዊና አስተዳደር ዘርፍ በባለፉት 9 ወራት አዳጊ የሆነ ለዉጥ ተመዝግቧል ፦ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
“የትግራይ ወጣት የፖለቲካ ሴራዎችን ተረድቷል፤ ከአሁን በኋላ የጦርነት መሣሪያ አይሆንም”፦ የቀድሞዋ አፈ-ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም