የሶማሊያ ፌደራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ለአንድ ቀን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል።
ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼኽ ሞሃሙድ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተቀብለዋቸዋል።
“ባለፈው አንድ ዓመት እየሰራንባቸው የቆየነውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ውይይቶች በመቀጠል ፍሬያማ ውይይት አድርገናል” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልዕክት።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ “የሃሳብ ልውውጣችን የወል የቅድሚያ ጉዳዮቻችንን ለመከወን ብሎም ለጠንካራ ግንኙነት፣ ቀጠናዊ መረጋጋት እና ልማት ያለንን ቁርጠኝነት በድጋሚ ያፀና ነበር” ማለታቸው ተዘግቧል።
More Stories
በማህበራዊ ዘርፍ የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያረጋጡ የልማት ስራዎች ተሰርተዋል፦ወ/ሮ ወሰነች ቶማስ
በክልሉ በኢኮኖሚ ፤በመሰረተ ልማት፤በማህበራዊና አስተዳደር ዘርፍ በባለፉት 9 ወራት አዳጊ የሆነ ለዉጥ ተመዝግቧል ፦ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ(ዶ/ር)
“የትግራይ ወጣት የፖለቲካ ሴራዎችን ተረድቷል፤ ከአሁን በኋላ የጦርነት መሣሪያ አይሆንም”፦ የቀድሞዋ አፈ-ጉባኤ ኬሪያ ኢብራሂም