ማሻ ፣ የግንቦት 15፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ‹‹ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፣ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል” በሚል መሪ ቃል ከሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ መምህራን ጋር የውይይት መድረክ ተካሂዷል ።
በዚህ መድረክ ላይ የተገኙት የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ደን አካባቢ ጥበቃና የአየር ንብረት ለውጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጂነር አስራት ገብረማርያም በመክፈቻ ንግግራቸው እንደገለፁት የከፍተኛ ትምህርት ተቋመት ትውልዱ በጥሩ ስነ ምግባርና በእውቀት ታንፀው ለሀገር መንግሥት ግንባታ ህደት ውስጥ የድርሻቸውን እንድወጡ ከማድረግ አንፃር ትልቅ ሚና እንዳላቸው ገልፀዋል ።
ከለውጡ ወድህ የተለያዩ ችግሮችን በማለፍ በብልፅግና እሳቤ ዘርፈ ብዙ ድሎች እየተመዘገቡ ይገኛል ያሉት የቢሮ ኃላፊዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትም ድሎችን ለማስቀጠል በምደረገው ጥረት ውስጥ የድርሻቸውን እንድወጡ ነው የተናገሩት ።
በመድረኩ የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ የቴፒ ካምፓስ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ከተማ ‹‹ትውልድ በመምህራን ይቀረፃል፣ ሀገር በትምህርት ይበለጽጋል የሚል የመወያያ ሰነድ ባቀረቡበት ወቅት በመማር ማስተማር ህደት ያሉትን ችግሮች ለይቶ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ከማስቀመጥ አኳያ ትኩረት ልደረግ እንደምገባ ገልፀዋል ።
በመድረኩ የክልሉ ደን፣ አካባቢ ጥበቃና አየር ንብረት ለዉጥ ቁጥጥር ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ኢንጅነር አስራት ገብረማርያም ፣የሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ካምፓስ ስራ አስፈፃሚ አቶ መንግስቱ ከተማን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው የስራ ኃላፊዎችና መምህራኖች ተሳትፈዋል።
ዘጋቢ አስቻለው አየለ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች