ማሻ ፣ የግንቦት 11፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በካንሰር ህመም መጠቃታቸውን ጽ/ቤታቸው አስታውቋል።
የ82 አመቱ ጆ ባይደን በከባድ የፕሮስቴት ካንሰር መጠቃታቸውና በካንሰር የተጠቃው ህዋሳቸው ወደ አጥንታቸው መዛመቱ ተነግሯል።
የፕሬዚዳንቱ የካንሰር ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፥ በሚደረግላቸው የህክምና አማራጮች ዙሪያ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እየመከሩ ነው ሲል አሶሺየትድ ፕረስ ዘግቧል።
የወቅቱ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለጆ ባይደን ባስተላለፉት መልዕክት፥ በሁኔታው ማዘናቸውን ገልጸው ከህመማቸው በፍጥነት እንዲያገግሙ ተመኝተዋል።
ፋና
More Stories
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡
ኢራን በእስራኤል ጥቃት የተገደሉባት የኒውክሌር ሳይንቲስቶች ቁጥር 10 ደረሰ