ማሻ ፣ የግንቦት 10፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም)በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 34 ሺህ 258 ህጻናት የትምህርት ቤት ምገባ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ክልሉ በማህበረሰቡ እገዛ የትምህርት ቤቶች ምገባ ዘንድሮ መጀመሩን የቢሮው ምክትል ኃላፊና የመማር ማስተማርና ምዘና ዘርፍ ኃላፊ ደስታ ገነሜ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል ገልጸዋል።
በዚህም በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በአንደኛና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ልዩ ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች የምገባ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
በ278 ትምህርት ቤቶች 34 ሺህ 258 ተማሪዎች የትምህርት ቤት ምገባ ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸው÷ መርሐ ግብሩ ከማህበረሰቡ በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ሀብት በመሰብሰብ የሚፈጸም ነው ብለዋል።
በቀጣይም በልዩ ሁኔታ ማህበረሰቡን፣ ባለሃብቱን እንዲሁም መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በማሳተፍ የምገባ መርሐ ግብሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እየተሰራ መሆኑን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች