ማሻ ፣ የግንቦት 05፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት አራት ቀናት የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ የሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸውን የመጀመሪያ የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸውን በሳዑዲ አረቢያ ጀምረዋል።
ዛሬ ሪያድ የገቡት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡
የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት ዋነኛ ዓላማ ለአሜሪካ ኢኮኖሚ ትልቅ አዲስ ኢንቨስትመንትን ለማስፈን ያለመ ስለመሆኑ ተዘግቧል፡፡
በሳውዲ አረቢያ ቆይታቸው የሳውዲ-አሜሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የሚሳተፉት ፕሬዚዳንት ትራምፕ፤ ጉብኝታቸው በመጪው አርብ የሚጠናቀቅ መሆኑ ተመላክቷል።
Fana
More Stories
የአውሮፓ ህብረት ያወጣቸውን ደንቦች መሠረት በማድረግ የግብርና ምርቶች ከደን ጭፍጨፋ ነፃ ሆነው እንዲመረቱ ከማድረግ አንፃር የግብርና ባለሙያዎች ሚና የጎላ እንደሆነ ተገለፀ ።
ትራምፕ ቲክ ቶክን የሚገዙ የአሜሪካ ባለሀብቶች ማግኘታቸውን ገለፁ
ሩሲያ እና ህንድ በጦር መሳሪያ አቅርቦት ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ እንደሚሰሩ አስታወቁ፡፡