May 13, 2025

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸውን በሳዑዲ ጀመሩ

ማሻ ፣ የግንቦት 05፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሚቀጥሉት አራት ቀናት የሁለትዮሽ ውይይት ለማድረግ የሁለተኛው የስልጣን ዘመናቸውን የመጀመሪያ የመካከለኛው ምስራቅ ጉብኝታቸውን በሳዑዲ አረቢያ ጀምረዋል።

ዛሬ ሪያድ የገቡት ፕሬዚዳንት ትራምፕ ከሀገሪቱ መሪ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡

የፕሬዚዳንቱ ጉብኝት ዋነኛ ዓላማ ለአሜሪካ ኢኮኖሚ ትልቅ አዲስ ኢንቨስትመንትን ለማስፈን ያለመ ስለመሆኑ ተዘግቧል፡፡

በሳውዲ አረቢያ ቆይታቸው የሳውዲ-አሜሪካ የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ የሚሳተፉት ፕሬዚዳንት ትራምፕ፤ ጉብኝታቸው በመጪው አርብ የሚጠናቀቅ መሆኑ ተመላክቷል።

Fana