ማሻ ፣ የሚያዝያ 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የኩፍኝ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት ለመስጠት ለሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ስልጠና እየሰጠ ነዉ።
በሸካ ዞን ጤና መምሪያ የእናቶችና ህጻናት ጤናና ስርዓተ ምግብ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተገኝ ገቦ ከግንቦት ስድስት እስከ አስራ አምስት ቀን 2017 ዓ.ም ለተከታታይ 10 ቀናት እድሜያቸው ከዘጠኝ ወር እስከ አምስት አመት ለሆናቸዉ ህጻናት የኩፍኝ በሽታን መከላከያ ክትባት እንደሚሰጥ ገልጸዋል።
ይህንንም ክትባት በአስፈላጊው ሁነታ ለማዳረስ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸው የተገለጽ ሲሆን ከነዚህም አንዱ እየተሰጠ ያለዉ የአሰልጣኞች ስልጠና መሆኑ ተመላክቷል።
እ.አ.አ በ2023 በተደረገዉ ጥናት በአለማችን እድሜያቸው ከ15 አመት በታች የሆኑና የኩፍኝ በሽታ ክትባት ያልወሰዱ ህጻናት 95 በመቶ በሽታ ላይ እንደሚወድቁ የሸካ ዞን ጤና መምሪያ የክትባት ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ገረመው ጭቶ ስልጠና በሰጡበት ወቅት ገልጸዋል።
በዚህ የክትባት ጊዜ ዉስጥ በዞኑ ባሉ እድሜያቸው ከ5 አመት በታች የሆኑ 41ሺህ 47 ህጻናትን ለመከተብ መታቀዱም ተመላክቷል።
የኩፍኝ በሽታ ለተለያዩ በሽታዎች ከማጋለጥ ባሻገር እስከሞት ድረስ የሚያደርስ መሆኑን ወላጆች በመገንዘብ ልጆቻቸውን እንዲያስከትቡም ጥሪ አቀርቧል።
ለሶስት ቀናት በሚሰጠው ስልጠና ላይ የሁሉም መዋቅር የጤና ጽ/ቤት ሀላፊዎች፣ በዘርፉ የጤና ባለሙያዎች፣ እንድሁም የዞን ጤና ማናጅመንት አባላትና ለሎች ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ይገኛሉ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች