ማሻ ፣ የመጋቢት 24፣ 2017 (ማሻ ኤፍ ኤም) ይህን የገለፁት የሸካ ዞን ልዩ የአዳሪ ትምህርት ማስጀመሪያ መረሃ ግብር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በቴፒ ከተማ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የመመዘኛ ፈተና አልፈው በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ አዳር ትምህርት ለመማር ከመጡት ተማሪዎች መካከል አንዳንዶቹ እንደገለፁት ይህ አድል መፈጠሩ የተሻለ ውጤት በማስመዝገብ ተወዳዳሪ እንድሆኑ እንደሚያግዛቸው ነው ።
ትኩረታችን በተሻለ እውቀት ወደ ተሻለ ደረጃ መድረስ ነው ያሉት ተማሪዎቹ አሁንሥ በየደረጃው የሚገኙ ባለድርሻ አካላት ድጋፍና ክትትል ስራዎችን እንድያጠናክሩ ጠይቀዋል ።
የተማሪ ወላጆችም በበኩላቸው የዞን መንግሥትና በየደረጃው የሚገኙ አካላት ይህን እድል በማመቻቸቱ አመስግነው ልጆቻቸውን በተለየ መልኩ ክትትል እንደሚያደርጉ ገልጸዋል ።
ብቁና ተወዳዳሪ የሆኑ ተማሪዎችን ለማፍራት የአዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ተናግረው የዘርፉን ስራ ለመደገፍ የበኩላቸውን እንደሚወጡ ጠቁመዋል ።
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች