ማሻ፣ ጥር 5፣ 2017 (ደሬቴድ ማሻ ቅርንጫፍ) በሚቀጥሉት ቀናቶች በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት መጠንና የደመና ሽፋን መጨመር እንደሚኖር የኢትዮጵያ ሚቲዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
በሚቀጥሉት ቀናቶች ከሚጠናከሩት የአየር ሁኔታ ክስተቶች ላይ በመነሳት በጥቂት የመካለኛው፣ በምሥራቅ፣ በሰሜን ምሥራቅ፤ በሰሜን ምዕራብ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ የሀገሪቱ አካባቢዎች ላይ አንጻራዊ የእርጥበት መጠንና የደመና ሽፋን መጨመር እንደሚኖር የትንበያ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘም የደቡብ ኦሮሚያ፣ ሲዳማ፣ ደቡብ ምዕራብ እና የምዕራብ አካባቢዎች ላይ ከቀላል እስከ መካከለኛ መጠን ያለው ዝናብ እንሚያገኙም ነው የኢንስቲትዩቱ መረጃ የሚያመላክተው፡፡
በሌላ በኩል አሁን ላይ እየተስተዋለ ያለው የበጋው ደረቅ፣ ጸሀያማ እና ነፋሻማው የአየር ሁኔታ በሚቀጥሉት ቀናትም ቀጣይነት እንደሚኖረው አሀዛዊ የትንበያ መረጃዎች ይጠቁማሉ ተብሏል፡፡
(ኤፍ ኤም ሲ)
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች