በሶስት አህጉራት የሚገኙት አዲስ አባል ሀገራቱ ቤላሩስ፣ ቦልቪያ፣ ኢንዶኖዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ኩባ፣ ማሌዥያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤከስታን መሆናቸው ታውቋል፡፡
የአዲስ አባል ሀገራቱ የአባልነት ጥያቄ ቀደም ሲል በሩሲያ ካዛን በተካሄደው 16ኛው የብሪክስ የመሪዎች ጉባኤ ላይ መፅደቁ ነው የተገለፀው፡፡
የብሪክስ አባል ለመሆን ከ30 በላይ ሀገራት ጥያቄ አቅርበው እንደነበር የተገለፀ ሲሆን አዲሶቹ ዘጠኝ አባል ሀገራቱ በብሪክስ መሪዎች ተገምገመው የአባልነት ጥያቄቸው ተቀባይነት ማግኘቱ ተመላክቷል፡፡
በቅርቡም ተጨማሪ አራት ሀገራት ብሪክስን ይቀላቀላሉ ተብሏል፡፡
በብራዚል፣ ሩሲያ፣ ህንድ፣ ቻይና እና ደቡብ አፍሪካ የተመሰረተው የብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን በፈረንጆቹ 2024 ኢትዮጵያን ጨምሮ አራት ሀገራትን በአባልነት መቀበሉ ይታወሳል።
አዳዲስ አባል ሀገራት መቀላቀላቸውን ተከትሎም 9 አባላት የነበሩት ብሪክስ የኢኮኖሚ ቡድን የአባላቱን ቁጥር ወደ 18 ከፍ ማድረጉን ኢራን ፕሬስ እና አር ቲ ዘግበዋል፡፡
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች