በኦሮሚያ ክልል መንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም ስምምነት በመፈጸማቸው የሰራዊቱ አባላት ወደ ካምፕ መግባት መጀመራቸው ይታወቃል።የኦሮሚያ ክልል የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተደረሰውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት የሰላም አማራጭን በመቀበሉ ከፍተኛ ደስታ እንደተሰማው ገልጿል።በጫካ የቀሩ የሰራዊቱ አባላትም ፈጥነው ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጡም ጥሪውን አስተላልፏል።ሰላም እንዲሰፍን የሃይማኖት አባቶች ጸሎት እና ምህላን ሲያደርጉ እንደነበር ያስታወሰው መግለጫው፤ በቀጣይነትም ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ጉባኤው የሰላም ግንባታ ላይ አበክሮ እንደሚሰራ አረጋግጧል።
ፋና
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች