በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተጀመረውን የኮሪደር ልማት ስራ አጠናክሮ ለማስቀጠል የተቀናጀ ርብርብ እንደሚያስፈልግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ። ርዕሰ መስተዳድሩ የኮሪደር ልማት ስራን በክልሉ በሚገኙ ሁሉም ከተሞች ተግባራዊ ማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮችና የዝግጅት ሂደት ላይ ያተኮረ ውይይት በአርባምንጭ ከተማ እያካሄዱ ነው። አቶ ጥላሁን ከበደ በዚህ ወቅት፣ ከተሞች ለነዋሪዎቻቸው ምቹና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ የኮሪደር ልማት ስራን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል። የተሻለ ከተማ ለቀጣይ ትውልድ ለማስረከብ እየተደረገ ላለው ሂደት የኮሪደር ልማት ስራ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ጠቅሰው፤ ለዚህም የከተማ ነዋሪዎችና የስራ አመራሩ ቁርጠኝነት እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። በውይይቱ የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሰተፉ መሆኑን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
በክልሉ የተጀመረውን የኮሪደር ልማት አጠናክሮ ለማስቀጠል የተቀናጀ ርብርብ ያስፈልጋል – አቶ ጥላሁን ከበደ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች