የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሀገር ዕድገት እና ብልፅግና ወሳኝ ድርሻ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
አቶ አሕመድ ሺዴ በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል የተለያዩ ክፍሎች ከተውጣጡ የሰራዊቱ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ በሰጡት ማብራሪያ÷ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቁም ባለፈ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ይህም የኢትዮጵያን ዕድገት እና ብልፅግናን ወደ ተሻለ ከፍታ እንደሚያሸጋግር ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው÷ በተቋሙ ያሉ የሰራዊቱ አመራሮች የመንግስትን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በበቂ ሁኔታ መረዳታቸው ቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲመሩ እንደሚያስችል መጥቀሳቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች