የገንዘብ ሚኒስቴር ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ዕቃዎችን ወደ ሀገር ማስገባትን በተመለከተ ለጉምሩክ ኮሚሽንና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ሰርኩላር አስተላልፏል።በዚህም ወደ ሀገር እንዳይገቡ በሕግ ክልከላ ከተደረገባቸው የነዳጅ አውቶሞቢሎች እና የፀጥታና ደህንነት ዕቃዎች ውጪ ሌሎች ዕቃዎች ያለ ውጭ ምንዛሬ ክፍያ (በፍራንኮ ቫሉታ) ወደ ሀገር እንዲገቡ በመንግሥት የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ ይኸው ተግባራዊ እንዲደረግ አሳስቧል።መንግሥት በቅርቡ ተግባራዊ ባደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ፤ የውጭ ምንዛሬ ተመን በገበያው አማካኝነት እንዲወሰን ማድረጉ እና ይኸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል።
EBC
More Stories
አዲሱ የማዕድንና ኢንዱስትሪ ትስስር
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካ አቪዬሽን ኢንዱስትሪ የጀርባ አጥንት መሆኑን በተግባር እያረጋገጠ ነው
የሸካ ህዝቦች ልማት ማህበር የጀመረው የሰንበት ገቢያ በበዓል ወቅት ከሚፈጠረው የዋጋ ንረት ታድጎናል ሲሉ የሸካ ዞን ማሻ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ።