በፎክስ ኒውስ አዘጋጅነት በሚካሄደው የምርጫ ክርክር ላይ ተመልካቾች እንዲታደሙ ተፈቅዷል
ሁለተኛው ዙር ክርክር የምርጫውን አሸናፊነት ይወስናሉ ከሚባሉ ግዛቶች መካከል አንዷ በሆነችው ፔንሴልቬንያ ይካሄዳል
የሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ ባይደንን ተክተው የዴሞክራት እጩ እንደሚሆኑ ከሚጠበቁት ካማላ ሃሪስ ጋር በሁለተኛው ምርጫ ክርክር ለመሳተፍ ተስማምተዋል፡፡
በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የተካሄደው የመጀመርያ ዙር ክርክር የባይደንን የዴሞክራት እጩነት አስከፍሏል፡፡
በሲኤንኤን አዘጋጅነት ያልተመልካች በዝግ ስቱድዮ በተደረገው ክርክር ሀሳባቸውን በቅጡ መግለጽ ሲሳናቸው የታዩት ጆ ባይደን ከእጩነት እንዲነሱ ተቃውሞ በርትቶባቸው ከምርጫው እራሳቸውን ማግለላቸው የሚታወስ ነው፡፡
ለ90 ደቂቃ በተካሄደው ክርክር ዶናልድ ትራምፕ አንዳንድ ከእውነታነት ከራቁ ሃሳቦቻቸው ጭምር በባይደን ላይ ብልጫ እንደወሰዱ ብዙዎች ተስማምተዋል፡፡
More Stories
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች
የአራዳ ፓርክ የነዋሪዎችን ሰብአዊ ክብር ያስቀደመ ፕሮጀክት ነው – ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የግድያ ሙከራ ተደረገባቸው