ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ስልጠና በዛሬው ዕለት በመደመር ትውልድ እና የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ አንኳር መርሆዎች ላይ አተኩሮ ተካሂዷል። በመደመር መንገድ በውጭ ግንኙነት ስራዎች ባለፉት አመታት በተገኙ ስኬቶች እና የተግባር ለውጦች ዙሪያ ለአምባሳደሮቹ ገለፃ ተደርጓል። መደመር አገር በቀል እሳቤ መሆኑን በመገንዘብ በዲፕሎማሲው መስክ ሃገራዊ ክብርን እና ጥቅምን ለማስጠበቅ በትጋት ሊሰራ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ ዓለምአቀፍ አሰላለፍን በመገንዘብ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን በማስቀደም መሰረታዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መድረኩን በአወያይነት መምራታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች