የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ የምስራቅ አፍሪካ ተጠባባቂ ሞተራይዝድ ሻለቃ አሁን ላይ ያለበትን ዝግጁነት ጎብኝተዋል። ፊልድ ማርሻሉ በጉብኝታቸው ሞተራይዝድ ሻለቃው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስታንዳርድ መሰረት ዝግጁነት ላይ እንደሚገኝ መመልከታቸውን ተናግረዋል። ሞተራይዝድ ሻለቃው በተሟላ የሰው ሀይልና ቴክኖሎጂ ቁመና ላይ እንደሚገኝ የተናገሩት ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ፤ ሻለቃው ለማንኛውም ተልዕኮ ዝግጁ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻላቸውንም ገልፀዋል። ኢትዮጵያ ለአፍሪካ በተለይም ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምና መረጋጋት ትልቅ አበርክቶ እንደነበራትም ፊልድ ማርሻሉ አስታውሰዋል።
ኢትዮጵያ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላም መረጋገጥ በሙሉ ዝግጁነት ላይ እንደምትገኝ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ገለፁ
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች