የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ከሃይማኖት አባቶች እና በክልሉ ከሚገኙ ሁሉም ዞኖች ከተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች እና ተፅኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር በወላይታ ሶዶ ከተማ በመወያየት ላይ ይገኛሉ፡፡ መድረኩ “የአባቶች ሚና በልዩነት ለተዋበ ጠንካራ የህዝቦች አንድነት” በሚል መሪ ቃል ነዉ እየተካሄደ የሚገኘው። ክልሉ የሰላም የመቻቻል እና የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየተደረገ ላለው ጥረት የሀገር ሽማግሌዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል። በውይይቱ ከርዕሰ መስተዳድሩ በተጨማሪ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች፤ የዞን አመራሮች፤ የሃይማኖት አባቶች፤ የሀገር ሽማግለዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙዪኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች