ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን በማልማት ተረጂነትን ለማስቀረት የጀመረችውን ግብ ለማሳካት አመራሩ በቁርጠኝነት ሊሠራ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡የፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ አመራሮች “ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለተሟላ ሀገራዊ ክብር፣ ነጻነት እና ሉዓላዊነት” በሚል መሪ ሐሳብ እየተወያዩ ነው፡፡በውይይቱም ከተረጂነት አስተሳሰብ መላቀቅ እና በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ በአጽንኦት ተገልጿል፡፡የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት÷ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ለመሸጋገር እንደ ሀገር ያሉ እምቅ ሃብቶችን በአግባቡ መጠቀም ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል፡፡ተረጂነትን ማስቀረት እንደሚቻልም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም የልማት ሥራዎች የተመዘገቡ ውጤቶች ማሳያ መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡የሀገር ሉዓላዊነት ምልዑ የሚሆነው የተረጂነት አስተሳሰብን በማስወገድ እና ምርታማነትን በእጅጉ በማሳደግ ራስን የመቻል ግብ ሲረጋገጥ መሆኑን አመላክተው÷ ከዚህ አኳያ አመራሩ ትልቅ ኃላፊነት አለበት ብለዋል።የዛሬው ውይይት ዓላማም አመራሩ ከተረጂነት ለመላቀቅና ምርታማነትን ለማሳደግ የመሪነት ሚናውን በአግባቡ እንዲወጣ መግባባት ለመፍጠር ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
FBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች