የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኳታር ዶሃ የሚገኘው የዶክ ሕክምና ማዕከል መስራች በሆኑት ዶ/ር ኢማኑኤል ቶሎሳ ከተመራ የልዑካን ቡድን አባላት ጋር ተወያይተዋል። የሕክምና ማዕከሉ በኢትዮጵያ የጤና ዘርፍ በኢንቨስትመንት መሰማራት በሚችልበት ሁኔታ ላይ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጓል።ማዕከሉ በዓይነቱ ልዩ የሆነ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ የአጥንት ህክምና ማዕከል በኢትዮጵያ ለማቋቋም ፍላጎት እንዳለው ተገልጿል። ዶክ በኳታር ከኦርቶፔዲክ፣ ሩማቶሎጂ፣ ኒውሮሎጂ፣ ኒውሮፊዚዮሎጂ፣ ፊዚዮቴራፒ፣ ካይሮፕራክቲክ እና የጥርስ ሕክምና ጋር የተያያዙ የምርምራ እና የሕክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ትልቁ የጤና ማዕከል መሆኑን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ቴፒ ግቢ አዘጋጅነት የተካሄደው14ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ጉባኤ ተጠናቀቀ ።
ማዕከሉ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ውስጥ 21ሺ 5መቶ ቶን በላይ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን በኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን የቴፒ ምርት ጥራት ምርምርና ሰርትፍኬሽን ማዕከል አስታወቀ።
አሜሪካ ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት 25 ቢሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ አጣች